ወ/ሮ ሰርካለም ቦጋለ:- የስራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ

የኢንስቲትዩት የአመለካከት ለውጥና የደንበኞች አያያዝ ላይ ስልጠና በ2016 ዓ.ም

የኢንስቲትዩት የአመለካከት ለውጥና የደንበኞች አያያዝ ላይ ስልጠና በ2016 ዓ.ም

የኢንስቲትዩት የአመለካከት ለውጥና የደንበኞች አያያዝ ላይ ስልጠና በ2016 ዓ.ም

Raeesh
ወ/ሮ ሰርካለም ቦጋለ

የስራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ

የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑ ስድስት ስራ አስፈጻሚዎች ሲኖሩ እነዚህም የተቋማችንን ዋና ተግባራትን በብቃትና በቅልጥፍና በመደገፍ ተቋማችን ስትራቴጂካዊ ግብ ለመምታት እንዲችል የተደራጁ ናቸዉ፡፡ የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ በዉስጡ የስትራቴጂክ ነክ ጉዳዩች ሥራ አስፈጻሚ ፤ የብቃትና የሰዉ ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ፤የግዥና ፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ፤ የተቋማዊ ለዉጥ ሥራ አስፈጻሚ፤ የመሰረታዊ አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ፤ ኢንፎርሜሽን ኮምንኬሽን ቴክኖሎጂ ሥራ አስፈጻሚ ክፍሎችን የያዘ ነዉ፡፡ እነዚህ እያንዳንዳቸዉ የስራ ክፍሎች በስራ አስፈጻሚ የተደራጁ ሆነዉ የተቋሙን ኮር ተግባራት ለማቀላጠፍ በተቻለ ቅልጥፍና እና ብቃት ስራዉን የሚከዉን ዘርፍ ነዉ፡፡

በ2016 ዓ.ም በጀት አመት የተቋማችን አመታዊ እቅድ ከእስትራቴጂክ እቅዱ ላይ በመርኮዝ በተቋሙ የሚገኙ መሪ ስራ አስፈጻሚዎችን እና የዳይሬክተር ጽ/ቤት በማስተባበር የተቋማዊ ለዉጥ ሥራ አስፈጻሚ አማካኝነት ተዘጋጅቶል፡፡ በክፍላቸን የሚገኘዉ የብቃትና የሰዉ ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ በዚህ በጀት አመት በተቋሙ አዲስ መዋቅርን መሰረት በማድረግ በብቁ የሰዉ ሀብት እንዲደራጅ ለማድረግ እቅድ በመያዝ ተፈጻሚ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም የሰዉ ሀብት ልማት ላይ በ2016 ዓ.ም እቅድ በመያዝ የተቋሙን ባለሞያዎች ለማብቃት የተለያዩ ዉጤትን መሰረት ያደረጉ ስልጠናዎች በማቀድ እያስፈጸመ ይገኛል፡፡
የስትራቴጂክ ነክ ጉዳዩች ሥራ አስፈጻሚ የተቋሙን የአስር አመት እስትራቴጂክ እቅድ በመመርኮዝ የአጭርና የረጅም ግዜ እቅዶችን መማዘጋጀት እንዲሁም የእያንዳንዱን የስራ ክፍል በጥልቀት በማጥናት እየሰራ ይገኛል፡፡የመሰረታዊ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ በ2016 ዓ.ም የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ በማቀድ ስራዉን እየተገበረ ይገኛል፡፡ የኢንፎርሜሽን ኮምንኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ በ2016 ዓ.ም የበጀት አመት በተቋሙ የተተገበሩ የቴክኖሎጂ ዉጤቶችን ባማከለ ሁኔታ በማቀድ ጀምሯል፡፡ በተጨማሪም አዲስ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች ለመዘርጋት እንዲሁም ከአጋር ተቋማት ጋር በማበር የሚተገበሩ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች ላይ እየሰራ ይገኛል፡፡