አቶ ጌታቸው መንግስቴ
አስተዳደራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
የኢንስቲትዩቱን የ3 ዓመት(2018-2020) ፍኖተ ካርታ በሚመለከት በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው መንግስቴ የሁኔታ ትንተናና መነሻ ሀሳቦች፣ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫና ግቦች እንዲሁም የትግበራ፣ክትትልና ግምገማ ማዕቀፍ ላይ ሰፋ ያለ ገለፃ ተደርጎ የተለያዩ ሀገራት ልምድና ተሞክሮዎችን በማቅረብ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ከሰራተኞችና ኃላፊዎች ሀሳቦችና አስተያየቶች ተሰጥተውበት ከመድረኩ በቂ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፡፡
የስትራቴጂክ ነክ ጉዳዩች ሥራ አስፈጻሚ የተቋሙን የአስር አመት እስትራቴጂክ እቅድ በመመርኮዝ የአጭርና የረጅም ግዜ እቅዶችን መማዘጋጀት እንዲሁም የእያንዳንዱን የስራ ክፍል በጥልቀት በማጥናት እየሰራ ይገኛል፡፡የመሰረታዊ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ በ2016 ዓ.ም የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ በማቀድ ስራዉን እየተገበረ ይገኛል፡፡ የኢንፎርሜሽን ኮምንኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ በ2016 ዓ.ም የበጀት አመት በተቋሙ የተተገበሩ የቴክኖሎጂ ዉጤቶችን ባማከለ ሁኔታ በማቀድ ጀምሯል፡፡ በተጨማሪም አዲስ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች ለመዘርጋት እንዲሁም ከአጋር ተቋማት ጋር በማበር የሚተገበሩ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች ላይ እየሰራ ይገኛል፡፡
